ማሊ 90 የማዕድን ፈቃዶችን ሰረዘች
18:19 30.10.2025 (የተሻሻለ: 18:24 30.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ማሊ 90 የማዕድን ፈቃዶችን ሰረዘች
ይህ ውሳኔ በዓለም አቀፍ የማዕድን ኩባንያዎች ተቀጥያዎች የተገኙ ፈቃዶችን መሰረዝን ያካትታል ሲል የምዕራባውያን መገናኛ ብዙኃን ይፋዊ አዋጅ ጠቅሶ ዘግቧል።
በሪፖርቱ መሰረት ፍቃድ የተሰረዘባቸው ኩባንያዎች፦
አፍሪካ ማይኒንግ ኤስ.ኤ.አር.ኤል.፤
አልባብ ማይኒንግ፤
ፕሮዲጂ ሪሶርስስ ሊሚትድ፤
ዋፊ ማይኒንግ ኤስ.ኤ.አር.ኤል. እና ሌሎችም።
ይህ እርምጃ ከ2015 እስከ 2022 ባለው ጊዜ ውስጥ ለብረት ማዕድን፣ ለወርቅ፣ ለቦክሳይት እና ለሌሎች ማዕድናት ፍለጋ የተሰጡ ፈቃዶች ላይ ያነጣጠረ ነው ሲል የዜና አውታሩ አስታውቋል።
እንዲህ ዓይነቱ ፖሊሲ የማዕድን ዘርፉን በጠንካራ ሕጎች ይበልጥ ጥብቅ ለማድረግ ያለመና ከበርካታ የአፍሪካ መንግሥታት አጠቃላይ ራዕይ ጋር የሚጣጣም ነው ሲል መገናኛ ብዙኃኑ አክሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X