የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የባቡር ክፍሎች እና መለዋወጫዎች ማምረቻ ማዕከል ሊያቋቁም ነው

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የባቡር ክፍሎች እና መለዋወጫዎች ማምረቻ ማዕከል ሊያቋቁም ነው
የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የባቡር ክፍሎች እና መለዋወጫዎች ማምረቻ ማዕከል ሊያቋቁም ነው - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.10.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ የምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የባቡር ክፍሎች እና መለዋወጫዎች ማምረቻ ማዕከል ሊያቋቁም ነው

ለዚህም ድርጅቱ ከደቡብ አፍሪካው ፊዛ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ጋር ስምምነት ተፈራርሟል።

መግባቢያው በሀገሪቱ ያለውን የባቡር መለዋወጫ እጥረት በመቅረፍ፣ የውጭ ምንዛሬ በማስቀረት እና ገበያውን በማጠናከር፤ ምርቶችን ለአፍሪካ ሀገራት ለማቅረብ ያስችላል ሲል ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል፡፡

የስምምነቱ ማዕቀፎች፦

በባቡር ጉዳዮች ላይ የቴክኒክ ድጋፍ ማግኘት፣

ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማትና ኢንቨስተሮች ጋር ትስስር መፍጠር፣

የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች መስጠት እና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ በትብብር መሥራት።

ፊዛ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በደቡብ አፍሪካ፣ ህንድ፣ በመካከለኛው ምስራቅና በአሜሪካ የባቡር አካላት እና መለዋወጫ እንደሚያቀርብ ተመላክቷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0