የትራምፕ ሌሎች ሀገራት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እየሞከሩ ነው የሚለው ንግግር የሩሲያን ቡሬቬስትኒክን ለመጥቀስ ከሆነ መረጃው የተሳሳተ ነው - ክሬምሊን
13:19 30.10.2025 (የተሻሻለ: 13:24 30.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የትራምፕ ሌሎች ሀገራት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እየሞከሩ ነው የሚለው ንግግር የሩሲያን ቡሬቬስትኒክን ለመጥቀስ ከሆነ መረጃው የተሳሳተ ነው - ክሬምሊን
በዲሚትሪ ፔስኮቭ የተሰጡ ሌሎች ቁልፍ መግለጫዎች፦
🟠 ትራምፕ ስለ ኒውክሌር ሙከራ የሰጡትን መግለጫ በተመለከተ፤ አሜሪካ ሉዓላዊ ሀገር በመሆኗ ሉዓላዊ ውሳኔዎችን የመወሰን መብት አላት።
🟠 አሜሪካ እስካሁን ስለ አዲሱ የስታርት ስምምነት ምንም አይነት ትርጉም ያለው ሀሳብ አላቀረበችም፤ አዲሱ የስታርት ስምምነት እጣ ፈንታ እና የኒውክሌር ሙከራ የተለያዩ ጉዳዮች ናቸው።
🟠 አሜሪካ የኒውክሌር ሙከራ እቅዷን በተመለከተ ለሩሲያ አላሳወቀችም።
🟠 ሞስኮ ስለ ቡሬቬስትኒክ እና ፖሳይዶን ሙከራዎች የተላለፈው መረጃ ለትራምፕ በትክክል እንደደረሰ ተስፋ ታደርጋለች።
🟠 ክሬምሊን አዲስ ዙር የጦር መሳሪያ ውድድር ተጀምሯል ብሎ አያምንም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X