https://amh.sputniknews.africa
የስፑትኒክ ፕሮ የሚዲያ ትምህርታዊ ጉባኤ በኢትዮጵያ ተካሄደ
የስፑትኒክ ፕሮ የሚዲያ ትምህርታዊ ጉባኤ በኢትዮጵያ ተካሄደ
Sputnik አፍሪካ
‘ስፑትኒክፕሮ’ በዓለም አቀፉ የዜና ኤጀንሲ ስፑትኒክ የተጀመረ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ትምህርት ፕሮጀክት ነው። በሩሲያ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛ የመገናኛ ብዙኃን ሥራ አስኪያጆች፣ ባለሙያዎች እና ግንባር ቀደም የኤጀንሲው ባለሙያዎች ለጋዜጠኞች፣ ለፕሬስ... 30.10.2025, Sputnik አፍሪካ
2025-10-30T12:02+0300
2025-10-30T12:02+0300
2025-10-30T12:02+0300
ዜና
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/0a/1e/2036012_0:101:1080:709_1920x0_80_0_0_8b1b00ecb9da00b07bcc7d86a7bb8fd1.jpg
‘ስፑትኒክፕሮ’ በዓለም አቀፉ የዜና ኤጀንሲ ስፑትኒክ የተጀመረ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ትምህርት ፕሮጀክት ነው። በሩሲያ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛ የመገናኛ ብዙኃን ሥራ አስኪያጆች፣ ባለሙያዎች እና ግንባር ቀደም የኤጀንሲው ባለሙያዎች ለጋዜጠኞች፣ ለፕሬስ ኦፊሰሮች፣ ለጦማሪዎች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ልዩ ሴሚናሮች፣ ንግግሮች እና የማስተርስ ትምህርቶች የሚሰጡበት ልዩ ፕሮግራም ነው።የስፑትኒክ ፕሮ ተናጋሪዎች በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የመገናኛ ብዙኃን የልህቀት ማዕከል የትምህርት ፕሮግራም ሥር ለጋዜጠኞች፣ ለተማሪዎች እና ለአካዳሚክ ባለሙያዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡የስፑትኒክ ዓለም አቀፍ ትብብር ዳይሬክተር ቫሲሊ ፑሽኮቭ፤ ስለ ሩሲያ የመገናኛ ብዙኃን ምህዳር ዝርዝር ጉዳዮች እና በዘመናዊ ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ውስጥ ስላሉ ዋና ዋና አዝማሚያዎች ለታዳሚዎች ንግግር አድርገዋል፡፡ በጆሃንስበርግ የስፑትኒክ ቢሮ ኃላፊ ቪክቶር አኖኪን፤ በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ስላሉ የሐሰት ዜናዎች ሀሳቦችን አጋርተዋል።ከ50 በላይ ተሳታፊዎች በዌቢናሩ ላይ በመገኘት ስለ ሩሲያ የመገናኛ ብዙኃን አወቃቀር፣ የዜጎች ጋዜጠኝነት እድገት፣ በደቡባዊ ዓለም የመገናኛ ብዙኃን ትብብር እና የሐሰት ዜናዎች መከላከያ ዘዴዎችን በተመለከት ጥያቄዎችን አቅርበዋል።የፕሮግራሙ አዘጋጆች የስፑትኒክ ንግግር አድራጊዎችን ከፍተኛ የእውቀት ደረጃ እና ሙያዊ ብቃት አፅንዖት ሰጥተው፤ በመገናኛ ብዙኃን ማዕከሉ የትምህርት ፕሮጀክቶች ዙሪያ ቀጣይ ትብብሮች እንደሚኖሩ ተስፋቸውን ገልጸዋል።ኢትዮጵያ፤ የመገናኛ ብዙኃን ሙያዊ ብቃት ደረጃን በላቀ ሁኔታ ለማዳበር እና የሀገሪቱን የመገናኛ ብዙኃን ገጽታ የማሳደግ ግቦችን ያነገበ ብሔራዊ የመገናኛ ብዙኃን የልህቀት ማዕከሏን በቅርቡ አስመርቃለች። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጋዜጠኞችን አቅም በተለያዩ መንገዶች ለመገንባት የሚያስችል ዘመናዊ ማዕከል ለማቋቋም ይህንን ብሔራዊ ተነሳሽነት ወስዷል። ባለሥልጣኑ የኢትዮጵያን የመገናኛ ብዙኃን ምህዳር የሚቆጣጠር፣ የሚከታተል እና የሚመራ ገለልተኛ የሕዝብ ተቋም ነው።
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
2025
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜናዎች
am_ET
Sputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
https://cdn.amh-img.sputnikglobe.com/img/07e9/0a/1e/2036012_0:0:1080:810_1920x0_80_0_0_b6a3b2576a50d038d9ad1af19552f558.jpgSputnik አፍሪካ
feedback.africa@sputniknews.com
+74956456601
MIA "Rossiya Segodnya"
ዜና
‘ስፑትኒክፕሮ’ በዓለም አቀፉ የዜና ኤጀንሲ ስፑትኒክ የተጀመረ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ትምህርት ፕሮጀክት ነው። በሩሲያ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛ የመገናኛ ብዙኃን ሥራ አስኪያጆች፣ ባለሙያዎች እና ግንባር ቀደም የኤጀንሲው ባለሙያዎች ለጋዜጠኞች፣ ለፕሬስ ኦፊሰሮች፣ ለጦማሪዎች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ልዩ ሴሚናሮች፣ ንግግሮች እና የማስተርስ ትምህርቶች የሚሰጡበት ልዩ ፕሮግራም ነው።
የስፑትኒክ ፕሮ ተናጋሪዎች በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የመገናኛ ብዙኃን የልህቀት ማዕከል የትምህርት ፕሮግራም ሥር ለጋዜጠኞች፣ ለተማሪዎች እና ለአካዳሚክ ባለሙያዎች ገለጻ አድርገዋል፡፡
የስፑትኒክ ዓለም አቀፍ ትብብር ዳይሬክተር ቫሲሊ ፑሽኮቭ፤ ስለ ሩሲያ የመገናኛ ብዙኃን ምህዳር ዝርዝር ጉዳዮች እና በዘመናዊ ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች ውስጥ ስላሉ ዋና ዋና አዝማሚያዎች ለታዳሚዎች ንግግር አድርገዋል፡፡ በጆሃንስበርግ የስፑትኒክ ቢሮ ኃላፊ ቪክቶር አኖኪን፤ በመገናኛ ብዙኃን ውስጥ ስላሉ የሐሰት ዜናዎች ሀሳቦችን አጋርተዋል።
ከ50 በላይ ተሳታፊዎች በዌቢናሩ ላይ በመገኘት ስለ ሩሲያ የመገናኛ ብዙኃን አወቃቀር፣ የዜጎች ጋዜጠኝነት እድገት፣ በደቡባዊ ዓለም የመገናኛ ብዙኃን ትብብር እና የሐሰት ዜናዎች መከላከያ ዘዴዎችን በተመለከት ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
"በበየነ መረብ ውይይቶች ላይ ሀገራዊ ልምዶቻቸውን እና የዘርፉ ተጨባጭ ማሳያዎችን በማጋራት የመወያያ ርዕሶችን ስለሚያዳብሩ፤ የዓለም አቀፍ እንግዶች ተሳትፎ ለፕሮግራሞቻችን ወሳኝ ናቸው" ሲሉ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የመገናኛ ብዙኃን የልህቀት ማዕከል አማካሪ አቶ አንተነህ ፀጋዬ ተናግረዋል፡፡
የፕሮግራሙ አዘጋጆች የስፑትኒክ ንግግር አድራጊዎችን ከፍተኛ የእውቀት ደረጃ እና ሙያዊ ብቃት አፅንዖት ሰጥተው፤ በመገናኛ ብዙኃን ማዕከሉ የትምህርት ፕሮጀክቶች ዙሪያ ቀጣይ ትብብሮች እንደሚኖሩ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ፤ የመገናኛ ብዙኃን ሙያዊ ብቃት ደረጃን በላቀ ሁኔታ ለማዳበር እና የሀገሪቱን የመገናኛ ብዙኃን ገጽታ የማሳደግ ግቦችን ያነገበ ብሔራዊ የመገናኛ ብዙኃን የልህቀት ማዕከሏን በቅርቡ አስመርቃለች። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጋዜጠኞችን አቅም በተለያዩ መንገዶች ለመገንባት የሚያስችል ዘመናዊ ማዕከል ለማቋቋም ይህንን ብሔራዊ ተነሳሽነት ወስዷል። ባለሥልጣኑ የኢትዮጵያን የመገናኛ ብዙኃን ምህዳር የሚቆጣጠር፣ የሚከታተል እና የሚመራ ገለልተኛ የሕዝብ ተቋም ነው።