የምዕራባውያን ድርጊቶች በዩሬዥያ ደህንነት ላይ የሚደረገውን መደበኛ ውይይት እያደናቀፉ ነው - ላቭሮቭ

ሰብስክራይብ

የምዕራባውያን ድርጊቶች በዩሬዥያ ደህንነት ላይ የሚደረገውን መደበኛ ውይይት እያደናቀፉ ነው - ላቭሮቭ

የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከሚንስክ የዩሬዥያ የፀጥታ ኮንፈረንስ በኋላ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የተናገሯቸው ቁልፍ መግለጫዎች፦

◾ ሞስኮ ፑቲን ባቀረቡት የኒው ስታርት ስትራቴጂካዊ የጦር መሳሪያ ቅነሳ ስምምነት ሀሳብ ላይ ከዋሽንግተን ይፋዊ እና አዎንታዊ ምላሽ እየጠበቀች ነው፡፡

◾ ኒው ስታርትን ስለማራዘም ለረጅም ጊዜ ጀምሮ ምንም አይነት ንግግር አልተደረገም፡፡

◾ በመሠረታዊነት ኒው ስታርትን የሚተካ አዲስ ስምምነት እውን ለማድረግ በሩሲያ-አሜሪካ መካከል የተለየ ግንኙነት እንዲኖር ይጠይቃል፡፡

◾ ሩሲያ የፑቲን-ትራምፕ ስብሰባ ተጨባጭ ውጤቶችን እንደሚያስገኝ ዋስትናዎች ያስፈልጓታል፡፡

◾ ሩሲያ የቡሬቬስትኒክ የክሩዝ ሚሳኤልን ከሞከረች በኋላ “ሁሉም ፀጥ ብሏል”፡፡

◾ ዶናልድ ትራምፕ ለኪዬቭ አገዛዝ ተጨማሪ መሳሪያዎችን ሳይሆን ዘላቂ ሰላምን እንደሚፈልጉ ሩሲያ ተስፋ ታደርጋለች፡፡

◾ ሞስኮ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ ከአሜሪካ ጋር ለሚኖር ትብብር ዝግጁ ነች፤ ነገር ግን ዋሽንግተን ቅድሚያ አልሰጠችውም፡፡

◾ ምዕራባውያን ከደቡብ ካውካሰስ ሀገራት ጋር የሚያደርጉትን ውይይት እነሱን ከሩሲያ ለመለየት ይጠቀሙበታል፤ ሞስኮ እንዲህ ያሉ ሙከራዎችን ትመክታለች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ሙሉ መግለጫ ይከታተሉ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0