ኢትዮጵያ አምስት ጂኦፓርኮችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በእጩነት አቀረበች
14:14 28.10.2025 (የተሻሻለ: 15:24 28.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ አምስት ጂኦፓርኮችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በእጩነት አቀረበች
ይህ ተነሳሽነት ተፈጥሯዊ ሀብቶቹን ከማሳወቅ ባለፈ ጂኦቱሪዝምን ለማልማት እና በመላ ሀገሪቱ የቱሪዝም መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ያለመው ሰፊ ስትራቴጂ አካል መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ ተናግረውል፡፡
የተመረጡት ስፍራዎች፦
ቡታጅራ-ስልጤ አካባቢ፣
ሶፍ ዑመር ዋሻ፣
ደናክል እና የኤርታሌ እሳተ ገሞራን ጨምሮ የአፋር ዝቅተኛ ሥፍራ፣
የሰሜን ተራሮች እና
የገረዓልታ ተራሮች ናቸው።
በአሁኑ ወቅት በዩኔስኮ ከተመዘገቡ 229 ዓለም አቀፍ ጂኦፓርኮች ውስጥ አብዛኛዎቹን አውሮፓ እና እስያ ሲይዙ አፍሪካ ሁለት ብቻ በማስመዝገብ በዘርፉ ያላት ውክልና አነስተኛ ነው፡፡
ኢትዮጵያ በልየታ በእጩነት ያቀረበቻቸው ሀብቶችም ይህን በማስተካከል ሚዛናዊነት ለማምጣት ይረዳል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X