ኢትዮጵያ አምስት ጂኦፓርኮችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በእጩነት አቀረበች
14:14 28.10.2025 (የተሻሻለ: 15:24 28.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ አምስት ጂኦፓርኮችን በዩኔስኮ ለማስመዝገብ በእጩነት አቀረበች
ይህ ተነሳሽነት ተፈጥሯዊ ሀብቶቹን ከማሳወቅ ባለፈ ጂኦቱሪዝምን ለማልማት እና በመላ ሀገሪቱ የቱሪዝም መሠረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ያለመው ሰፊ ስትራቴጂ አካል መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ስለሺ ግርማ ተናግረውል፡፡
የተመረጡት ስፍራዎች፦
ቡታጅራ-ስልጤ አካባቢ፣
ሶፍ ዑመር ዋሻ፣
ደናክል እና የኤርታሌ እሳተ ገሞራን ጨምሮ የአፋር ዝቅተኛ ሥፍራ፣
የሰሜን ተራሮች እና
የገረዓልታ ተራሮች ናቸው።
በአሁኑ ወቅት በዩኔስኮ ከተመዘገቡ 229 ዓለም አቀፍ ጂኦፓርኮች ውስጥ አብዛኛዎቹን አውሮፓ እና እስያ ሲይዙ አፍሪካ ሁለት ብቻ በማስመዝገብ በዘርፉ ያላት ውክልና አነስተኛ ነው፡፡
ኢትዮጵያ በልየታ በእጩነት ያቀረበቻቸው ሀብቶችም ይህን በማስተካከል ሚዛናዊነት ለማምጣት ይረዳል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X