በሉቭረ ሙዚየም የጌጣጌጥ ስርቆት የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተዘገበ
15:54 26.10.2025 (የተሻሻለ: 16:04 26.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሉቭረ ሙዚየም የጌጣጌጥ ስርቆት የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተዘገበ
ትናትና ምሽት ተይዘዋል ሲል የምርመራው ምንጭ የሆኑ ሁለት ሰዎች ለፈረንሳይ ሚዲያ ተናግረዋል፤ ይህም የቀድሞ ዘገባዎችን የሚያረጋግጥ ነው።
▪ አንዱ ተጠርጣሪ ከምሽቱ 5 ሰዓት አካባቢ በቻርለስ ደ ጎል አውሮፕላን ማረፊያ ዓለም አቀፍ በረራ ሊሳፈር ሲል በቁጥጥር ስር ውሏል።
▪ ሁለተኛው ደግሞ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ፓሪስ አካባቢ መያዙ ተዘግቧል።
በፓሪስ የሚገኘው ሉቭረ ሙዚየም የከበሩ ጌጣጌጦች ከተሰረቁ ከሁለት ቀናት በኋላ ረቡዕ ለጎብኚዎች ዳግም ተከፍቷል።
ጥቅምት 9 ቀን ሌቦች ሉቭር ሙዚየምን ሰብረው በመግባት ከ23ቱ የ"ናፖሊዮን እና እቴጌይቱ" ስብስብ ውስጥ ዘጠኝ ጌጣጌጦችን ሰርቀዋል። የተሰረቁት እቃዎች ቀደም ሲል የፈረንሳይ ንግስቶችና እቴጌዎች የነበሩ አክሊሎች፣ የጆሮ ጌጦች፣ የአንገት ጌጦች እና ሌሎች ጌጣጌጦች ይገኙበታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X