የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ማስፋፊያው አውሮፕላን ለማምረት ወጥኗል
19:37 25.10.2025 (የተሻሻለ: 19:44 25.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአገር ውስጥ የኢንዱስትሪ ማስፋፊያው አውሮፕላን ለማምረት ወጥኗል
አየር መንገዱ ከአፍሪካ ትልቁ አየር መንገድነት ሚናው ተሻግሮ ወደ አውሮፕላን ማምረቻ ዘርፍ ለመግባትና የኢንዱስትሪ አሻራውን ለማጠናከር እየተዘጋጀ ነው።
የቦይንግ አፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሄኖክ ተፈራ ሻውል፣ የአየር መንገዱ ዕቅድ በመጪዎቹ ዓመታት የአውሮፕላን ክፍሎችን በቀጥታ ለቦይንግ ማቅረብ እንደሚያስችለው ለአገር ውስጥ የግል ሚዲያ ገልጸዋል።
“የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አገር ውስጥ የአውሮፕላን ማምረት ሥራ ተጨባጭ እርምጃዎችን እየወሰደ ሲሆን፣ በጊዜ ሂደትም ለቦይንግ ግብዓቶችን ያቀርባል” ሲሉ ለሚዲያው አክለዋል።
ለዚህ ጥረት መሠረት የሆነው፣ እ.ኤ.አ. በ2023 ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን እና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ጋር በመተባበር ቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ሥራ የጀመረው ፋብሪካ ፦
የአውሮፕላን አካሎችን፣
የሙቀት መከላከያ አልባሳት እና
የኤሌክትሪክ ሽቦ ማቀፊያዎች ይጠቀሳሉ፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X