አረቢካ ቡና በታሪክ ከፍተኛውን ዋጋ አስመዘገበ
16:25 24.10.2025 (የተሻሻለ: 16:34 24.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አረቢካ ቡና በታሪክ ከፍተኛውን ዋጋ አስመዘገበ
ግዙፉ የፊውቸር ኮንትራቶች (ወደፊት የሚካሄዱ የንግድ ውሎች) አዘጋጅ ከሆነው "ከኢንተርኮንቲኔንታ" ምርት ገበያ በተገኘው መረጃ መሠረት፤ ለታኅሣሥ 2018 ዓ.ም አቅርቦት የሚውል የአረቢካ ቡና ዋጋ በ1.29 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፤ በአንድ ፓውንድ (0.45 ኪሎ ግራም) 4.263 ዶላር (በአንድ ቶን 9 ሸህ 398 ዶላር ገደማ) ደርሷል።
በዚያ የግብይት ጊዜ ውስጥ፣ አመላካቾች እንዳሳዩት፤ በአንድ ፓውንድ 4.349 ዶላር ነክቷል፤ ይህም ከአንድ ቶን 9,588 ዶላር ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡
ከዚህ ቀደም የተመዘገበው ከፍተኛ ዋጋ በመስከረም 5 ቀን 2015 ዓ.ም ነበር። በዚያ ወቅት ዋጋው በፓውንድ 4.1385 ዶላር ወይም ወደ በአንድ ቶን 9 ሺህ 124 ዶላር አካባቢ ነበር።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X