የዓለም ገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን ጠንካራ የሪፎርም ፕሮግራም ትግበራ አደነቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየዓለም ገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን ጠንካራ የሪፎርም ፕሮግራም ትግበራ አደነቀ
የዓለም ገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን ጠንካራ የሪፎርም ፕሮግራም ትግበራ አደነቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.10.2025
ሰብስክራይብ

የዓለም ገንዘብ ድርጅት የኢትዮጵያን ጠንካራ የሪፎርም ፕሮግራም ትግበራ አደነቀ

የኢትዮጵያ ልዑክ ከአይ ኤም ኤፍ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ እና የአፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዋሽንግተን ውይይት አድርጓል።

በዚህ ወቅት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ በማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት፣ የሥራ እድል ፈጠራ እና የዜጎችን ኑሮ ማሻሻል ላይ ያተኮሩ ጠንካራ የሪፎርም ሥራዎች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥት የገንዘብ አስተዳደርን ለማጠናከር፣ የሀገር ውስጥ ሃብት ማሰባሰብን ለማጎልበት እና ቁልፍ መዋቅራዊ የሪፎርም ሥራዎች ለማፋጠን ቁርጠኛ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አይ ኤም ኤፍ ለኢትዮጵያ ለሚያደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ያመሠገኑም ሲሆን አበዳሪው ተቋም በበኩሉ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ለውጥ ለመርዳት ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0