በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የአሸባሪዎች ቡድን ጥቃት መክሸፉን የሀገሪቱ ጦር አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የአሸባሪዎች ቡድን ጥቃት መክሸፉን የሀገሪቱ ጦር አስታወቀ
በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የአሸባሪዎች ቡድን ጥቃት መክሸፉን የሀገሪቱ ጦር አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.10.2025
ሰብስክራይብ

በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የአሸባሪዎች ቡድን ጥቃት መክሸፉን የሀገሪቱ ጦር አስታወቀ

ጽንፈኛ እስላማዊ ቡድኖች በሀገሪቱ ሰሜን ምስራቅ በአራት አካባቢዎች ጥቃቶችን ለመፈጸም ሞክረዋል ሲሉ የሰሜን ምስራቅ የጋራ ግብረ ኃይል የሚዲያ መረጃ መኮንን ሳኒ ኡባ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።

“በሁሉም ቦታዎች ወታደሮቹ ጸንተው በመቆም በጀግንነት ተዋግተዋል፤ ጥቃቶቹንም በሙያዊ ብቃት በመመከት በአሸባሪዎቹ ላይ ከባድ፣ ወሳኝ እና ደቋሽ ጥቃት ፈጽመዋል” ሲሉ አስረግጠዋል።

ጥቃቱ የተጀመረው ሌሊቱን በቦርኖ እና ዮቤ ግዛቶች በሚገኙ በርካታ ወታደራዊ ቦታዎች ላይ መሆኑ ተጠቁሟል። የ "ሀዲን ካይ" ኦፕሬሽን ወታደሮች 50 ጥቃት አድራሾችን መግደልና መሳሪያዎቻቸውን መማረክ ችለዋል ሲሉ ኡባ አክለዋል።

ጥቃት አድራሾቹ የየትኛው አሸባሪ ቡድን አባላት እንደሆኑ ግን አልገለጹም።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0