መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በጋምቤላ ክልል ሥራ ጀመረ
19:16 23.10.2025 (የተሻሻለ: 19:24 23.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በጋምቤላ ክልል ሥራ ጀመረ
የተቋማትን አገልግሎት በአንድ ቦታ መስጠት መቻል ለዜጎች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ወጪ ቆጣቢ አሠራርን ለመዘርጋት ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ተናግረዋል።
ማዕከሉ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ጉዞ ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው እና ሙስናና ብልሹ አሠራሮችን በማስቀረት ረገድም የጎላ ፋይዳ ስላለው ለስኬታማነቱ በትኩረት እንደሚሠራ አንስተዋል።
በክልል ደረጃ የተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በከተማ አስተዳደርና በዞን መዋቅሮችም የማስፋት ሥራ እንደሚከናወን ተመላክቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

