ኢትዮጵያ የቪዛ ግዜ ገደብ አሳልፈዋል ባለቻቸው ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ እርምጃ ወሰደች
19:05 23.10.2025 (የተሻሻለ: 19:14 23.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የቪዛ ግዜ ገደብ አሳልፈዋል ባለቻቸው ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ እርምጃ ወሰደች
ወደ ሀገሪቱ የሚመጡ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ሕግ አክብረው እንዲንቀሳቀሱ የስርዓት ማስከበር እርምጃዎች መወሰዳቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት አስታውቀዋል፡፡
በዚህ ሂደት የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ያሳለፉ የውጭ ሀገር ዜጎችን በመቅጣት ሕጋዊ መስመር እንዲይዙ ተደርጓል ማለታቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የቪዛ ስርዓትን አክብረው በማይንቀሳቀሱ የውጭ ሀገራት ዜጎች ላይ እርምጃ እንደምትወስድ ማስታወቋ የሚታወስ ነው፡፡
በሌላ በኩል ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ በሕገ ወጥ ሰንሰለት የተሠማሩ 26 ሰዎች ተጠያቂ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X