ኢትዮጵያ የቪዛ ግዜ ገደብ አሳልፈዋል ባለቻቸው ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ እርምጃ ወሰደች
19:05 23.10.2025 (የተሻሻለ: 19:14 23.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የቪዛ ግዜ ገደብ አሳልፈዋል ባለቻቸው ከ36 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ላይ እርምጃ ወሰደች
ወደ ሀገሪቱ የሚመጡ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ሕግ አክብረው እንዲንቀሳቀሱ የስርዓት ማስከበር እርምጃዎች መወሰዳቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት አስታውቀዋል፡፡
በዚህ ሂደት የተሰጣቸውን የቪዛ ጊዜ ያሳለፉ የውጭ ሀገር ዜጎችን በመቅጣት ሕጋዊ መስመር እንዲይዙ ተደርጓል ማለታቸውን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል፡፡
ሀገሪቱ ከዚህ ቀደም የቪዛ ስርዓትን አክብረው በማይንቀሳቀሱ የውጭ ሀገራት ዜጎች ላይ እርምጃ እንደምትወስድ ማስታወቋ የሚታወስ ነው፡፡
በሌላ በኩል ከፓስፖርት አገልግሎት ጋር በተያያዘ በሕገ ወጥ ሰንሰለት የተሠማሩ 26 ሰዎች ተጠያቂ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X