የ2018 ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24 እንዲካሄድ ምክረ ሃሳብ ቀረበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየ2018 ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24 እንዲካሄድ ምክረ ሃሳብ ቀረበ
የ2018 ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24 እንዲካሄድ ምክረ ሃሳብ ቀረበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.10.2025
ሰብስክራይብ

የ2018 ብሔራዊ ምርጫ ግንቦት 24 እንዲካሄድ ምክረ ሃሳብ ቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ የሚካሄድበትን ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባደረገው ምክክር ለውይይት ማቅረቡ ተገልጿል፡፡

37 ተግባራት የሚከናወኑባቸውን ጊዜያት በቀን እና በወራት ከፋፍሎ ያስቀመጠው ቦርዱ ግንቦት 24 ድምፅ መስጫ፤ ሰኔ 3 ደግሞ ወጤት ይፋ ማድረጊያ ቀናት አድርጎ በረቂቅ የጊዜ ሰሌዳው ላይ አስቀምጧል፡፡

በረቂቅ የግዜ ሰሌዳው የተካተቱ ሌሎች ተግባራት፦

በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጮች ምዝገባ ከህዳር ወር አጋማሽ  የካቲት መጨረሻ፣

መደበኛው የመራጮች ምዝገባ ከየካቲት መጀመሪያ እስከ መጋቢት መጀመሪያ፣

በምርጫ የሚሳተፉ ዕጩዎች ምዝገባ ከታህሳስ መጀመሪያ እስከ ጥር መጀመሪያ፣

የምረጡኝ ቅስቀሳ ወይም የምርጫ ዘመቻ ከታህሳስ 10 እስከ ግንቦት 19፣

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀጣይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ከሚያደርጋቸው ውይይቶች በኋላ ይፋዊ የምርጫ ቀኑን እንደሚያሳውቅ ይጠበቃል፡፡

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0