ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የኮሪዶር አስተዳደር ባለሥልጣን ለማቋቋም ተስማሙ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የኮሪዶር አስተዳደር ባለሥልጣን ለማቋቋም ተስማሙ
ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የኮሪዶር አስተዳደር ባለሥልጣን ለማቋቋም ተስማሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.10.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የኮሪዶር አስተዳደር ባለሥልጣን ለማቋቋም ተስማሙ

ኢትዮጵያ፣ ጅቡቲ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኢጋንዳን ያቀፈው የ”ደሱ” ኮሪዶር አስተዳደር ባለሥልጣን ለመመስረት የሀገራቱ የጋራ ቴክኒካል ኮሚቴ እና የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተስማምተዋል፡፡

ላለፉት ለሁለት ቀናት በጅቡቲ ሲደረግ የቆየው የጋራ ውይይት የስምምነት ቃለ-ጉባኤ በመፈራረም መጠናቀቁን በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

ሀገራቱ ከሁለት ሳምንት በኋላ በኢትዮጵያ በመገናኘት የአስተዳደሩን ማቋቋሚያ ስምምነት ለመፈራረም ከመግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡

የ ”ደሱ” ኮሪደር በአራቱ ሀገራት መካከል የውጪ ንግድ መንገዶችን በቀላሉ ለማገናኘት፣ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አገልግሎትን ለማሳለጥ ያለመ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0