በኢትዮጵያ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ለገበያ ቀረቡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበኢትዮጵያ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ለገበያ ቀረቡ
በኢትዮጵያ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ለገበያ ቀረቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 22.10.2025
ሰብስክራይብ

በኢትዮጵያ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ ከባድ ተሽከርካሪዎች ለገበያ ቀረቡ

ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃላ/የተ/የግል ማኅበር ከቻይናው የከባድ መኪና አምራች ሻክማን ኩባንያ ጋር በጋራ በመሆን ተሽከርካሪዎቹን ለመጀመሪያ ግዜ ለኢትዮጵያ ገበያ አስተዋውቀዋል፡፡

ድርጅቱ ከሻክማን ኩባንያ በተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ መኪኖችን በመረከብ ኢትዮጵያ ውስጥ ለማቅረብ በትናንትናው ዕለት ስምምነት የፈፀመ ሲሆን በቅርቡም 150 ተሽከርካሪዎች እንደሚገቡ ተገልጿል።

ቤአኤካ በመጀመሪያ ዙር የምርት ምዕራፍ በሀገር ውስጥ 1 ሺህ 500 በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ለመገጣጠምም አቅዷል፡፡

በቅርቡ በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል የካሉብ የተፈጥሮ ጋዝ የመጀመሪያ ዙር ምረት መጀመሩን ተከትሎ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነዳጅ የሚጠቀሙ ከባድ መኪኖችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት እንደተከለከለ መግለጻቸው የሚታወስ ነው፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0