ኡጋንዳ ውስጥ በደረሰ ከባድ የመኪና አደጋ የ63 ሰዎች ህይወት አለፈ
12:40 22.10.2025 (የተሻሻለ: 12:54 22.10.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኡጋንዳ ውስጥ በደረሰ ከባድ የመኪና አደጋ የ63 ሰዎች ህይወት አለፈ
ሁለት አውቶብሶችና አራት መኪናዎች ላይ የደረሰው አደጋ፤ ረቡዕ ንጋት ዋና ከተማዋን ካምፓላን ከጉሉ ጋር በሚያገናኘው አውራ ጎዳና ላይ እንደተከሰተ ተገልጿል።
ፖሊስ አሳዛኙን ክስተት አስመልክቶ በሰጠው ማብራሪያ፤ አደጋው የአንዱ አውቶቡስ ሹፌር የጭነት መኪናን ለመቅደም ሲሞክር እንደደረሰ ጠቁሟል፡፡ በተመሳሳይ ጊዜ በተቃራኒ መስመር የነበረ ሌላ አውቶቡስም ተመሳሳይ የመቅደም ሙከራ ሲያደርግ እንደነበር አመልክቷል።
አውቶቡሶች ፊት ለፊት ተጋጭተዋል፡፡ የአንደኛው አውቶብስ አሽከርካሪ ግጭቱን ለማስወገድ ያደረገው እንቅስቃሴ በአቅራቢያ የነበሩ መኪኖች ቁጥጥር እንዲያጡ እና ለበርካታ ግዜ እንዲገለባበጡ አድርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
/ 




