“ሩሲያ አፍሪካውያን በነጻነት ፖሊሲያቸውን እንዲያወጡና እንዲተገብሩ የማድረግ ልምዱ አላት” - የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ“ሩሲያ አፍሪካውያን በነጻነት ፖሊሲያቸውን እንዲያወጡና እንዲተገብሩ የማድረግ ልምዱ አላት” - የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር
“ሩሲያ አፍሪካውያን በነጻነት ፖሊሲያቸውን እንዲያወጡና እንዲተገብሩ የማድረግ ልምዱ አላት” - የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.10.2025
ሰብስክራይብ

“ሩሲያ አፍሪካውያን በነጻነት ፖሊሲያቸውን እንዲያወጡና እንዲተገብሩ የማድረግ ልምዱ አላት” - የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር

በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ጌድዮን ጢሞቲዮስ እና የሩሲያ አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ መካከል ዛሬ በሞስኮ የተካሄደውን ውይይት አስመልክቶ ለስፑትኒክ አፍሪካ አስተያየታቸውን የሰጡት የፖለቲካ ሳይንስ ባለሙያው እንዳለ ንጉሴ፤ ለኢትዮጵያ የኢኮኖሚ፣ ኃይል እና ዲፕሎማሲ ውጥኖች የሩሲያ ድጋፍ ቁልፍ እንደሆነ ጠቁመዋል፡፡

“የአንድ ሀገር ዲፕሎማሲ በኢኮኖሚ መደገፍ አለበት፤ በኢነርጂ ነጻነት መደገፍ አለበት፤ ጥራት ባለው መከላከያ ኃይል መደገፍ አለበት፡፡ ከዚህ አንጻር እንግዲህ በዓለም ወሳኝ ድጋፍ ከሚሰጡ ሀገሮች ደግሞ ሩሲያ ከግንባር ቀደሞቹ አንዷ ናት፡፡ ስለዚህ ሩሲያ የኢትዮጵያን መከላከያ ለመደገፍ የወሰደችው ተነሳሽነት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ባስተማማኝ መልኩ እንዲተገበር፤ ነጻነቷንም የበለጠ እንድታስቀጥልና በሌሎች ሀገራት ለሚኖራት ክብርም ፋይዳው የላቀ ነው፡፡”

ላቭሮቭ ሩሲያ ‘ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎች’ የሚለውን መርህ ሁሌም ታከብራለች ሲሉ በዛሬው ስብሰባቸው ገልፀዋል፡፡ ባለሙያው በዚህ ዙሪያ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል

“የአፍሪካ ፍላጎት ችግሮቿን በራሷ ለመፍታት፤ ፖሊሲዎቿን በነጻነት እንድታወጣ ነው፡፡ ሩሲያም ቻይናም እንደዚህ አይነት ፖሊሲዎችን በመደገፍ ተግባራዊ በማድረግ ይታወቃሉ፡፡ ከዚህ አንጻር ፖሊሲን በነጻነት የማውጣት ችግር...ጣልቃ ገብነቱ ስላለ ሁልጊዜ የሆነ ቦታ ይሄዳል፣ ይቆማል፡፡ ይሄ እንዳይሆን የሩሲያ ድጋፍ በጣም አስፈላጊ ነው” ብለዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0