ማላዊ ነፃ ትምህርት እና ርሃብን ለመዋጋት የአደጋ ግዜ የምግብ አቅርቦት ይፋ አደርገች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱማላዊ ነፃ ትምህርት እና ርሃብን ለመዋጋት የአደጋ ግዜ የምግብ አቅርቦት ይፋ አደርገች
ማላዊ ነፃ ትምህርት እና ርሃብን ለመዋጋት የአደጋ ግዜ የምግብ አቅርቦት ይፋ አደርገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.10.2025
ሰብስክራይብ

ማላዊ ነፃ ትምህርት እና ርሃብን ለመዋጋት የአደጋ ግዜ የምግብ አቅርቦት ይፋ አደርገች

ከመጪው ጥር 2026 ጀምሮ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ለሁሉም የማላዊ ዜጎች ነፃ እንደሚሆን አዲስ ተሿሚው ፕሬዝዳንት ፒተር ሙታሪካ አስታውቀዋል።

"ወላጆች አሁን ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ላለመላክ ምንም ምክንያት አይኖራቸውም" ሲሉ የተናገሩት ሙታሪካ፤ ትምህርት ለብሔራዊ ልማት መሠረት መሆኑን ገልጸዋል።

በተመሳሳይ ስለ ሀገሪቱ የምግብ ቀውስ ያነሱት ፕሬዝዳንቱ፤ የምግብ እጥረት ላለባቸው ሰዎች የአስቸኳይ ጊዜ የምግብ አቅርቦት ከውጭ እንደሚገባ ይፋ አድርገዋል፡፡ መንግሥት ከአራት ሚሊዮን በላይ የምግብ እጥረት ያለባቸውን ሰዎች ለመመገብ 200ሺህ ቶን በቆሎ ከዛምቢያ እየገዛ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ፕሬዝዳንቱ ስምምነቱን ለመፈፀም "ሁሉም ነገር ዝግጁ" እንደሆነና የግብርና ሚኒስትሩም በዛምቢያ ቅድመ ዝግጅቶች እያጠናቀቁ እንደሚገኙ ለዜጎቻቸው አረጋግጠዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0