የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለከፍተኛ ደረጃ ምክክር እና ቴክኖሎጂ ጉብኝት ወደ ሞስኮ አቀኑ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለከፍተኛ ደረጃ ምክክር እና ቴክኖሎጂ ጉብኝት ወደ ሞስኮ አቀኑ
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለከፍተኛ ደረጃ ምክክር እና ቴክኖሎጂ ጉብኝት ወደ ሞስኮ አቀኑ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.10.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለከፍተኛ ደረጃ ምክክር እና ቴክኖሎጂ ጉብኝት ወደ ሞስኮ አቀኑ

ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ከሩሲያ አቻቸው ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ማክሰኞ እንደሚወያዩ ይጠበቃል ሲል በሩሲያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምንጭ ለስፑትኒክ ገልፀዋል።

ጉዞው ተጨማሪ ዲፕሎማሲያዊ ስብሰባዎችን እና በሩሲያ ዋና የፈጠራ ማዕከል ስኮልኮቮ ጉብኝትን ያካትታል ሲሉ ምንጩ አመልክተዋል።

ይህ ጉብኝት የሁለቱን ሀገራት የቅርብ ግዜ የጠበቀ እና የከፍተኛ ደረጃ ግንኙነት የሚያስቀጥል ነው።

🟠 በመስከረም ወር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሞስኮ የዓለም አቶሚክ ሳምንት ፎረም ላይ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ተገናኝተው ለቀጣይ ስብሰባቸው አዲስ አበባ እንዲመጡ ጋብዘዋቸዋል። ሁለቱ ወገኖች ለኢትዮጵያ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የድርጊት መርሃ-ግብርም ተፈራርመዋል።

🟠 ባለፈው ዓመት የካቲት ወር የሩሲያ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሊቀመንበር ቫለንቲና ማትቪዬንኮ ከኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ተገናኝተው የፑቲንን ሞቅ ያለ ሰላምታ አቅርበዋል። በጉብኝቱ የሁለትዮሽ እና ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር የጋራ ቁርጠኝነት በድጋሚ ተረጋግጧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0