የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የምግብ ዋጋ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ረሃብን ለመዋጋት ብሔራዊ ጥሪ አቀረቡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የምግብ ዋጋ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ረሃብን ለመዋጋት ብሔራዊ ጥሪ አቀረቡ
የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የምግብ ዋጋ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ረሃብን ለመዋጋት ብሔራዊ ጥሪ አቀረቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.10.2025
ሰብስክራይብ

የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት የምግብ ዋጋ እየጨመረ ባለበት በአሁኑ ወቅት ረሃብን ለመዋጋት ብሔራዊ ጥሪ አቀረቡ

በደቡብ አፍሪካ ከ15 እስከ 16 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በቂ የምግብ አቅርቦት እጥረት እንዳለባቸው ሲሪል ራማፎሳ በሳምንታዊ ሪፖርታቸው ገልጸዋል።

ድህነትን እና የምግብ እጦትን መቅረፍ የብሔራዊ አንድነት መንግሥት ቁልፍ ተግባር መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።

"ደቡብ አፍሪካ የምግብ እና የውሃ መብት በሕገ-መንግሥት ከተደነገገባቸው እና ዜጎች ይህን መብት እንዲያስከብሩ የሕግ ስርዓት ካስቀመጡ 29 ሀገራት ተርታ ትጠቀሳለች" ብለዋል።

በየዕለቱ ዘጠኝ ሚሊዮን ተማሪዎችን የሚመግበውን እንደ የትምህርት ቤት ምገባ ያሉ ፕሮግራሞችን ቢያነሱም ከፍተኛ የሥራ አጥነት እና የዋጋ ንረት የቤተሰቦችን በጀት እየተፈታተነ መምጣቱን ራማፎሳ ጠቁመዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0