ሐማስ አሜሪካን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሷል በማለት ያቀረበችበትን ክስ አስተባበለ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሐማስ አሜሪካን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሷል በማለት ያቀረበችበትን ክስ አስተባበለ
ሐማስ አሜሪካን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሷል በማለት ያቀረበችበትን ክስ አስተባበለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.10.2025
ሰብስክራይብ

ሐማስ አሜሪካን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሷል በማለት ያቀረበችበትን ክስ አስተባበለ

ፍልስጤማዊው ንቅናቄ በመግለጫው የሚከተሉትን ነጥቦችንም አስታውቋል፡-

በመሬት ላይ ያለው እውነታ እንደሚያሳየው የወራሪው አካል ባለሥልጣናት "በጋዛ ሰርጥ የወንጀል ቡድኖችን አደራጅተዋል፣ አስታጥቀዋል እንዲሁም በገንዘብ ደግፈዋል"።

ሐማስ የአሜሪካን አስተዳደር "የወራሪውን አካል ትርክት ማስተጋባት እንዲያቆም እና በምትኩ የተኩስ አቁም ስምምነትን መጣስ ላይ እንዲያተኩር" አሳስቧል።

በንቅናቄው ላይ የሚሰነዘሩት የሐሰት ክሶች "ከእስራኤል ፕሮፓጋንዳ ጋር የሚጣጣሙ እና የወራሪው አካል ባለሥልጣናት ለሚፈጽሟቸው ተከታታይ ወንጀሎችና ጥቃቶች እንደ ሽፋን ሆነው ያገለግላሉ"።

በትናንትናው ዕለት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት እንዳስታወቀው፤ አሜሪካ ስለ ሐማስ "በቅርቡ የሚፈፀም" የተኩስ አቁም ስምምነት ጥሰት ለጋዛ ሰላም ስምምነት ዋስትና ለሰጡ አገሮች አሳውቃ ነበር።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሐማስ አሜሪካን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሷል በማለት ያቀረበችበትን ክስ አስተባበለ
ሐማስ አሜሪካን የተኩስ አቁም ስምምነቱን ጥሷል በማለት ያቀረበችበትን ክስ አስተባበለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.10.2025
አዳዲስ ዜናዎች
0