ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በባሌ ዞን የሚገኘውን የወልመል ወንዝ የመስኖ ፕሮጀክት መረቁ
18:49 18.10.2025 (የተሻሻለ: 18:54 18.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በባሌ ዞን የሚገኘውን የወልመል ወንዝ የመስኖ ፕሮጀክት መረቁ
ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅሙ ወደ ተግባር ሲገባ 20 ሺህ ለሚሆኑ አርሶ አደሮች የሚያገለግል፣ 9 ሺህ 687 ሄክታር በላይ የእርሻ መሬት አስተማማኝ የመስኖ አቅርቦት ይኖረዋል ሲሉ ዐቢይ በማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ጽፈዋል።
የመስኖ ፕሮጀክቱ፦
የግብርና ምርታማነትን የሚያሳደግ፣
ለድርቅ የማይበገር ከባቢን የሚፈጥር እና
ለማኅበረሰቡ አዳዲስ የሥራ እድል የሚከፍት ነው ተብሏል።
ከኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ባሻገር የአካባቢውን የውሃ አስተዳደር ተቋማትን በማጠናከር፣ የአካባቢውን ሕዝብ ባለቤትነት በማሳደግ የወልወልን ወንዝ ዘላቂ አጠቃቀም በማሻሻል የተሻለ የምግብ ሉዓላዊነት ጠቀሜታ ያገለግላል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
