ናይጄሪያ ሥራ አጥነትን ለመዋጋት እና ከሥልጠና ወደ ሥራ በሚደረግ ሽግግር ያለውን ክፍተት ለመሙላት አዲስ የሠራተኛ ፕሮጀክት ይፋ አደረገች
18:46 16.10.2025 (የተሻሻለ: 18:54 16.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ ሥራ አጥነትን ለመዋጋት እና ከሥልጠና ወደ ሥራ በሚደረግ ሽግግር ያለውን ክፍተት ለመሙላት አዲስ የሠራተኛ ፕሮጀክት ይፋ አደረገች
የብሔራዊ የሥራ ማዕከል ፕሮጀክቱ በመላ አገሪቱ የሥራ ዕድሎችን ለመፍጠር የሚያስችሉ የሥራ ማዕከላትን ያካትታል ሲሉ የሥራና ስምሪት ሚኒስትር ዴኤታ ንኬይሩካ ኦንዬጄኦቻ ተናግረዋል።
አዲሱ ፕሮጀክት የሚከተሉትን ያካትታል፦
ሥራ ፈላጊዎችን ከሥራ ጋር የሚያገናኙ ዲጂታል መድረኮች፣
የሥራ ገበያ መረጃ ክትትል፣
የሙያ ምክር አገልግሎቶች።
“ግባችን ሥራ መፍጠር ብቻ ሳይሆን የሠራተኞችን መብት የሚጠብቁ፣ ፍትሐዊ ደመወዝ የሚያረጋግጡ እና የሥራ ገበያ አስተዳደርን የሚያጠናክሩ ሥርዓቶችን መገንባት ነው።” ሲሉ ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልፀዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የናይጄሪያን የሥራ ገበያ ሁኔታ ለማጠናከር የፕሬዝዳንት ቦላ ቲኑቡ የዳግም ተስፋ አጀንዳ ማዕቀፍ ቁልፍ አካል ነው ሲሉም አክለዋል።
በሰው ሠራሽ አስትተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X