አፍሪካ በባሕርተኞች ሥልጠና ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲኖራት መሥራት ይገባል - የዘርፉ ምሑር

ሰብስክራይብ

አፍሪካ በባሕርተኞች ሥልጠና ዓለም አቀፍ ዕውቅና እንዲኖራት መሥራት ይገባል - የዘርፉ ምሑር

አፍሪካዊያን በባሕር ኢንዱስትሪ ዘርፍ ያላቸውን ተጽዕኖ ለማሳደግ፤ መንግሥታት አኅጉሪቱ በዘርፉ ዓለም አቀፍ የብቃት ማረጋገጫ ዕውቅና በምታገኝበት አግባብ መሥራት እንዳለባቸው በናይጄሪያ የጆማሪን የባሕር ጥናት እና ምርምር ተቋም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኬኔት ኤፒዴል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"አሁን ላይ አፍሪካዊያን ባሕርተኞች የምንወስዳቸው ሥልጠናዎች በአብዛኛው በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና የላቸውም። ስለዚህም እያንዳንዱ የአፍሪካ ሀገር በዓለም አቀፉ የባሕር ኃይል ድርጅት ውስጥ ባሉ አጋሮች ላይ ግፊት ማድረግ አለበት" ብለዋል።

በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው አህጉር አቀፉ የማሪታይም ጉባኤ ላይ በርካታ ቁልፍ ተዋንያን በዘርፉ አንገብጋቢ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0