ማሊና ሩሲያ የ65 ዓመታት የወዳጅነትና ፍሬያማ ትብብር በጋራ አከበሩ
15:33 14.10.2025 (የተሻሻለ: 15:34 14.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ማሊና ሩሲያ የ65 ዓመታት የወዳጅነትና ፍሬያማ ትብብር በጋራ አከበሩ
ሞስኮና ባማኮ ጥቅምት 4 በሚውለው የሁለቱ ሀገራት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የምስረታ በዓል ላይ ትብብራቸውን ለማጠናከር ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
የማሊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላዬ ዲዮፕ በመተማመን፣ በጋራ መከባበር እና የበለጠ ፍትሐዊነት የሰፈነበት ባለብዙ ወገን የጋራ ራዕይ ላይ የተመሠረተ አጋርነትን እንደሚያፀኑ አጉልተው አንስተዋል።
ማሊ በ1960 ነፃነቷን ካገኘችበት ጊዜ ጀምሮ ከሩሲያ ድጋፍ ስታገኝ ቆይታለች፤ ይህም ትስስር በማሊ "የጋራ ትውስታ" ውስጥ ተቀርጿል ብለዋል፡፡
ሩሲያ በበኩሏ በሳህል ክልል አሸባሪነትን በመዋጋት ረገድ ቁልፍ ተዋናይ ከሆነችው ማሊ ጋር ወታደራዊና የቴክኒክ ትብብርን ማጎልበት ላይ ትኩረት እንደምታደርግ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ጠቁማለች።
በሩሲያ መሳሪያዎች እና አሠልጣኞች ድጋፍ የማሊ ኃይሎች በአክራሪ ቡድኖች ላይ ውጤታማ ዘመቻዎችን እያካሄዱ መሆኑን ሚኒስቴሩ አጽንዖት ሰጥቷል።
ባማኮ በአፍሪካ በተለይም በኢኮኖሚ ትብብር በሞስኮ ቅድሚያ የሚሰጣት አጋር እንደሆነችና ከማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ ጋር የሚሠራ የምክክር ማዕከል በሩሲያ የንግድ ምክር ቤት ውስጥ ለማቋቋም መታቀዱን ገልጿል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X