አሜሪካ ለኪዬቭ ማቅረብ የምትችለው ከ20 እስከ 50 የሚደርሱ ቶማሃውክ ሚሳኤሎች ብቻ ነው ተባለ
14:59 14.10.2025 (የተሻሻለ: 15:04 14.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ ለኪዬቭ ማቅረብ የምትችለው ከ20 እስከ 50 የሚደርሱ ቶማሃውክ ሚሳኤሎች ብቻ ነው ተባለ
ይህም ሀገሪቱ በአጠቃላይ 4 ሺህ 150 ያህል የቶማሃውክ ሚሳኤሎች ቢኖሯትም እንደሆነ የቀድሞ የፔንታጎን ባለሥልጣን ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
አቅርቦቶቹ በዩክሬን ግጭቱ ያለበትን ሁኔታ በጉልህ እንደማይለውጡትም በዘገባው ተመላክቷል፡፡
ይህ ግምገማ ፑቲን በጥቅምት ወር መጀመሪያ የተናገሩትን ግምት የሚያስተጋባ ነው።
የቶማሃውክ ሚሳኤሎች ለኪዬቭ ከተላለፉ ሩሲያ የአየር መከላከያ ስርዓቶቿን ታጠናክራለች ሲሉ የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቀደም ሲል ተናግረዋል። በተጨማሪም የእነዚህ ሚሳኤሎች አጠቃቀም ቀጥተኛ የአሜሪካ ወታደራዊ ተሳትፎ ከሌለ የማይቻል እንደሆነና ይህም የሞስኮ እና ዋሽንግተንን ግንኙነት ይበልጥ ውጥረት ውስጥ እንደሚከተው አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X