ኢትዮጵያን በአግባቡ የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ፈጠራዎችን ማስፋት ይገባል

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያን በአግባቡ የሚረዱ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ፈጠራዎችን ማስፋት ይገባል

አሁን ላይ ያሉ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት የቴክኖሎጂ ውጤቶች የኢትዮጵያን ቋንቋ፣ ባሕል፣ ታሪክ እና ሌሎች ጉዳዮችን ጠንቅቆ ከመረዳት አንጻር ክፍተት እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ስታርት አፕ ሥነ-ምሕዳር ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ ነብዩ ይርጋ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።

"ኢትዮጵያን የተመለከቱ የሰው ሠራሽ አስተውህሎት ውጤቶች ከእኛ ጋር በጣም የተጣጣሙ እንዳልሆኑ ታያለህ። ስለዚህም በዘርፉ ያለውን ውስንነት የሚሞሉ ሞዴሎችን መፍጠር አለብን" ብለዋል።

አቶ ነብዩ ይርጋ በኢትዮጵያዊ ግንዛቤ እና ምላሽ አሰጣጥ የተቃኘ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ምንነትንም አስረድተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0