ግብፅ የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሊሻን ለዶናልድ ትራምፕ ልታበረክት ነው
18:26 13.10.2025 (የተሻሻለ: 18:34 13.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ግብፅ የሀገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሊሻን ለዶናልድ ትራምፕ ልታበረክት ነው
ሽልማቱ ትራምፕ የጋዛ ጦርነት እንዲያበቃ ባደረጉት ወሳኝ ሚና እና ለሰላም ጥረቶችና ግጭት አፈታት ላበረከቱት አስተዋጽኦ እውቅና ለመስጠት የሚበረከትላቸው እንደሆነ የግብፅ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
ትራምፕ በጥቅምት ወር መጀመሪያ እስራኤል እና የፍልስጤም ቡድን ሃማስ በጋዛ ሰርጥ ያለውን ግጭት ለመፍታት የሰላም ዕቅዱን የመጀመሪያ ምዕራፍ ተግባራዊ ለማድረግ ስምምነት ላይ እንደደረሱ ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው።
በሌላ በኩል የእስራኤል ፕሬዝዳንት ኢሳቅ ሄርዞግ ለትራምፕ የሀገሪቱን ከፍተኛ የሲቪል ክብር፤ የፕሬዝዳንታዊ የክብር ሜዳሊያ፤ ለመሸለም መወሰናቸውን ጽህፈት ቤታቸው አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X