ትራምፕ ለእስራኤል ፓርላማ ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱትራምፕ ለእስራኤል ፓርላማ ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ትራምፕ ለእስራኤል ፓርላማ ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 13.10.2025
ሰብስክራይብ

ትራምፕ ለእስራኤል ፓርላማ ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦

🟠 በመካከለኛው ምስራቅ የሽብርና የሞት ዘመን አብቅቷል፣ ቀጣናውም “አዲስና ታሪካዊ ዘመን” እያየ ነው።

🟠 ያለ ልዩ ተደራዳሪው ዊትኮፍ፤ “ዓለም ሦስተኛ የዓለም ጦርነት ሊገጥማት ይችል ነበር።”

🟠 ዊትኮፍ ሞስኮን ከጎበኘ በኋላ ከፑቲን ጋር “ብዙ አስደሳች ነገሮችን” እንደተወያየ ሪፖርት አድርጓል።

🟠 በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ከማምጣት የዩክሬንን ግጭት መፍታት ቀላል ነው።

🟠 ራሳቸውን ተፈጥሯዊ ሰላም ፈጣሪ ሲሉ በመግለፅ፤ ጦርነቶችን በማስቆም እንደሚሳካላቸው አንስተዋል።

🟠 አሜሪካ ጦርነቶችን ለመጀመር ፍላጎት የላትም፤ ነገር ግን አስፈላጊ ከሆነ “ማንም አሸንፎ በማያውቀው ልክ” ታሸንፋለች።

🟠 የጋዛ ግጭት መቆም፤ “የፍልስጤማውያን የረዥም ጊዜ ቅዠት” እንዲያበቃ አድርጓል።

🟠 የኢራን የዩራኒየም ማበልጸጊያ ተቋማት ሳይወድሙ የጋዛ የሰላም ስምምነት እውን አይሆንም ነበር፡፡

🟠 ኢራን ከአሜሪካ ጋር “ስምምነት ላይ በመድረስ” ግንኙነቷን መደበኛ ለማድረግ ፈቃደኛነት እያሳየች ነው።

🟠 ከጋዛ ስምምነት በኋላ በዩክሬን ግጭት አፈታት ዙሪያ ትኩረት ለማድረግ አቅደዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0