ትራምፕ ለእስራኤል ፓርላማ ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
15:43 13.10.2025 (የተሻሻለ: 15:44 13.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ትራምፕ ለእስራኤል ፓርላማ ባደረጉት ንግግር የተናገሯቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 በመካከለኛው ምስራቅ የሽብርና የሞት ዘመን አብቅቷል፣ ቀጣናውም “አዲስና ታሪካዊ ዘመን” እያየ ነው።
🟠 ያለ ልዩ ተደራዳሪው ዊትኮፍ፤ “ዓለም ሦስተኛ የዓለም ጦርነት ሊገጥማት ይችል ነበር።”
🟠 ዊትኮፍ ሞስኮን ከጎበኘ በኋላ ከፑቲን ጋር “ብዙ አስደሳች ነገሮችን” እንደተወያየ ሪፖርት አድርጓል።
🟠 በመካከለኛው ምስራቅ ሰላም ከማምጣት የዩክሬንን ግጭት መፍታት ቀላል ነው።
🟠 ራሳቸውን ተፈጥሯዊ ሰላም ፈጣሪ ሲሉ በመግለፅ፤ ጦርነቶችን በማስቆም እንደሚሳካላቸው አንስተዋል።
🟠 አሜሪካ ጦርነቶችን ለመጀመር ፍላጎት የላትም፤ ነገር ግን አስፈላጊ ከሆነ “ማንም አሸንፎ በማያውቀው ልክ” ታሸንፋለች።
🟠 የጋዛ ግጭት መቆም፤ “የፍልስጤማውያን የረዥም ጊዜ ቅዠት” እንዲያበቃ አድርጓል።
🟠 የኢራን የዩራኒየም ማበልጸጊያ ተቋማት ሳይወድሙ የጋዛ የሰላም ስምምነት እውን አይሆንም ነበር፡፡
🟠 ኢራን ከአሜሪካ ጋር “ስምምነት ላይ በመድረስ” ግንኙነቷን መደበኛ ለማድረግ ፈቃደኛነት እያሳየች ነው።
🟠 ከጋዛ ስምምነት በኋላ በዩክሬን ግጭት አፈታት ዙሪያ ትኩረት ለማድረግ አቅደዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X