ኢትዮጵያውያን በክንዳችሁ ብርታት፤ ሠንደቅ ዓላማችሁን እና ሀገራችሁን መጠበቅ ይኖርባችኋል - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
12:40 13.10.2025 (የተሻሻለ: 12:44 13.10.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያውያን በክንዳችሁ ብርታት፤ ሠንደቅ ዓላማችሁን እና ሀገራችሁን መጠበቅ ይኖርባችኋል - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያውያን በክንዳችሁ ብርታት፤ ሠንደቅ ዓላማችሁን እና ሀገራችሁን መጠበቅ ይኖርባችኋል - ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ
18ኛው ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን ‘ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጲያ ሕዳሴ’ በሚል መሪ ሃሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ይገኛል፡፡
"ኢትዮጵያውያን በአዕምሮአችሁ ሰላምን ማፅናት በልባችሁ የተስፋን ወጋገን አጥብቆ መያዝ፣ በክንዳችሁ ብርታት ደግም ሠንደቅ ዓላምችሁን እና ሀገራችሁን መጠበቅ ይኖርባችኋል” ሲሉ ርዕስ ብሔር ታዬ አፅቀሥላሴ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በተከናወነው 18ኛው የሠንደቅ ዓላማ ቀን አከባበር ላይ ተናግረዋል፡፡
የሠንደቅ ዓላማ ቀን እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር፣ ክብርና ቃልኪዳን በልቡ የሚያድስበት፣ የጋራ ማንነነቱን የሚያጎላበትና የነገ ተስፋውን የሚያጸናበት ታላቅ ብሔራዊ ዕለት ነው ብለዋል፡፡
ብሔራዊ የሠንደቅ ዓላማ ቀን በአዋጅ ቁጥር 863/2006 አንቀጽ 2 መሰረት በየዓመቱ በጥቅምት ወር የመጀመሪያ ሰኞ ይከበራል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
