በደቡብ አፍሪካ-ዚምባብዌ ድንበር ላይ በደረሰ አስከፊ የአውቶቡስ አደጋ ከ40 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
11:49 13.10.2025 (የተሻሻለ: 11:54 13.10.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በደቡብ አፍሪካ-ዚምባብዌ ድንበር ላይ በደረሰ አስከፊ የአውቶቡስ አደጋ ከ40 በላይ ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን የክልል ባለሥልጣናትን ጠቅሰው እንደዘገቡት፤ እሁድ ምሽት ከመካዶ አቅራቢያ በኤን አንድ አውራ ጎዳና ላይ አንድ አውቶቡስ ተገልብጦ የሞት እና የአካል ጉዳት አስከትሏል።
አደጋው የደረሰው ከዚምባብዌ ድንበር 90 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ ሲሆን፤ የአውቶቡሱ ሹፌር መሪውን መቆጣጠር ባለመቻሉ ተሽከርካሪው ገደል ውስጥ መግባቱ ተጠቅሷል።
የድንገተኛ አደጋ አገልግሎት 38 የተረፉ ሰዎችን በአቅራቢያው ወደሚገኙ ሆስፒታሎች ሲያጓጉዙ የነፍስ አድን ቡድኖች ተጨማሪ ተጎጂዎችን መፈለግ መቀጠላቸውን ዘገባው አክሏል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
