የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያለማቸው ቴክኖሎጂዎች ፍትሕን ለማፋጠን ይረዳሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
12:23 12.10.2025 (የተሻሻለ: 12:24 12.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያለማቸው ቴክኖሎጂዎች ፍትሕን ለማፋጠን ይረዳሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ
ተቋሙ ፈጣን፣ ግልጽ እና ውጤታማ የሆነ ሥርዓት ለመገንባት በጽናት እየሠራ እንደሚገኝ የገለፁት የሀገሪቱ መሪ፤ የፍትሕ ተደራሽነት ለዜጎች እጅግ አስፈላጊ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ መሆኑን እውቅና ሰጥቷልም ብለዋል፡፡
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያለማቸው ቴክኖሎጂዎች፦
የፍርድ ሂደቶች በአግባቡ መቀዳታቸውን ለማረጋገጥ ድምጽን ወደ ጽሁፍ የሚቀይር እና በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያቆይ ስማርት የፍርድ ሥርዓት፣
የአውታረ መረብ ሥራ ማዕከል፣
የተቀናጀ የጉዳይ አሰተዳደር ሥርዓት፡፡
በአሁኑ ወቅት 24 የፌደራል ቅርንጫፎች በሥርዓቱ ተሸፍነዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “በቅርቡ ወደ ክልሎች እንደሚስፋፋ ተስፋ አለን” ሲሉ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደቶችን በጎበኙበት ወቅት ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/2
© telegram sputnik_ethiopia

2/2
© telegram sputnik_ethiopia
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
2/2
© telegram sputnik_ethiopia