ቬንዙዌላ እንድትወረር ለጠየቁ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሰጠ
17:59 10.10.2025 (የተሻሻለ: 18:04 10.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቬንዙዌላ እንድትወረር ለጠየቁ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ የኖቤል የሰላም ሽልማት ተሰጠ
የኖቤል ኮሚቴ ለቀድሞዋ የቬንዙዌላ የሕግ አውጪ እና ታዋቂ የተቃዋሚ ፓርቲ አባል ማሪያ ኮሪና ማቻዶ የኖቤል የሰላም ሽልማትን ሰጥቷል።
ሽልማቱ የሚሰጠው "ለአገራት ወንድማማችነት፣ ቋሚ የጦር ኃይሎችን ለማጥፋት ወይም ለመቀነስ እንዲሁም የሰላም ኮንግረሶችን ለማካሄድ እና ለማስተዋወቅ እጅግ ብዙ ሥራ ለሠሩ" ሰዎች ነው።
ቀደም ሲል የቬንዙዌላ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማቻዶ በቴሌቪዥን በተላለፈ ቃለ-ምልልሳቸው ላይ የካሪቢያኗ አገር ለምዕራቡ ዓለም "ስጋት" መሆኗን በመግለፅ አሜሪካ መራሽ "ጥቃት በቬንዙዌላ ላይ እንዲፈፀም" ያቀረቡትን ጥሪ አውግዟል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X