ኢትዮጵያ በሱዳን ግጭት ሳቢያ ከ98 ሺህ በላይ ተፈናቃዮችን መቀበሏን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኤጀንሲ አስታወቀ
14:59 10.10.2025 (የተሻሻለ: 15:04 10.10.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ በሱዳን ግጭት ሳቢያ ከ98 ሺህ በላይ ተፈናቃዮችን መቀበሏን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኤጀንሲ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ በሱዳን ግጭት ሳቢያ ከ98 ሺህ በላይ ተፈናቃዮችን መቀበሏን የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኤጀንሲ አስታወቀ
በሱዳን ሚያዝያ 15 ቀን 2023 የትጥቅ ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ፣ ኢትዮጵያ ደህንነትንና ጥበቃን የሚሹ በግዳጅ የተፈናቀሉ ግለሰቦችን በከፍተኛ ቁጥር ተቀብላለች።
በኤጀንሲው ሪፖርት መሠረት፣ እስከ 2025 ድረስ ወደ ድንበር አካባቢ ከገቡ 98 ሺህ 502 በላይ ሰዎች፦
🟠 76 ሺህ 120 የሚሆኑት አስቸኳይ ዓለም አቀፍ ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው ናቸው።
🟠 48,964 የሚሆኑት ደግሞ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በአሶሳ መቆየታቸውን ኤጀንሲው በሪፖርቱ አስታውቋል።
🟠 8,328 የሚሆኑት በ2025 ብቻ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ የሱዳን ስደተኞችን ናቸው፡፡
ይህ ሰብአዊ ፍሰት በምስራቅ አፍሪካ እየጨመረ የመጣውን መፈናቀል ተከትሎ ኢትዮጵያ በቀጣናዊ ጥበቃ ጥረቶች ውስጥ ያላትን ወሳኝ ሚና ያጎላል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X