ሶማሊያ የስዋሂሊ ቋንቋን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ በፍጥነት ትተገብራለች - ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ
11:25 09.10.2025 (የተሻሻለ: 11:34 09.10.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሶማሊያ የስዋሂሊ ቋንቋን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ በፍጥነት ትተገብራለች - ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶማሊያ የስዋሂሊ ቋንቋን በትምህርት ሥርዓት ውስጥ በፍጥነት ትተገብራለች - ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ
የምስራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ ውህደትን ለማሳደግ ስዋሂሊ ከሶማልኛ፣ ከአረብኛ እና ከእንግሊዝኛ ጎን ለጎን የሥራ እና የመማሪያ ቋንቋ ሆኖ ይተዋወቃል።
በምሥራቅ አፍሪካ ማኅበረሰቦች ጉባኤ (በኢኤኮን2025) ላይ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ የሶማሊያ ዩኒቨርሲቲዎች የስዋሂሊን ቋንቋ በማስተማር ረገድ መሪ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ በተለይም የሶማሊያ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ የቀዳሚነቱን ሚና እንዲወስድ አሳስበዋል።
የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስትር ፋራህ ሼክ አብዱልቃድር በበኩላቸው፣ መንግሥት ስዋሂሊን ለመግባቢያ፣ ለንግድ እና ለመማር ዋና ቋንቋ ለማድረግ አስቦ፣ ከቀጣናዊ ተቋማት ጋር በመተባበር በመላ አገሪቱ የሚሠራ የስዋሂሊ ቋንቋ ማዕቀፍ እየዘረጋ ነው።
የብሔራዊ የከፍተኛ ትምህርት ቦርድ እቅዱን ለመተግበር እንደ የምስራቅ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲዎች ማኅበር ካሉ ቀጣናዊ አካላት ጋር እየሠራ ነው።
ሀገሪቱ በጎርጎሮሳዊያኑ 2024 ስዋሂሊን በይፋ እንደ አንዱ የሥራ ቋንቋ አጽድቃለች።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X