ፕሬዝዳንት ፑቲን ለሦስት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ታጂኪስታን ገቡ
21:46 08.10.2025 (የተሻሻለ: 21:54 08.10.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፕሬዝዳንት ፑቲን ለሦስት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ታጂኪስታን ገቡ
በጉብኝቱ ወቅት የሩሲያው ፕሬዝዳንት በሁለተኛው የመካከለኛው እስያና ሩሲያ የመሪዎች ጉባኤ ላይ የሚሳተፉ ሲሆን የሲ.አይ.ኤስ. (የነፃ መንግሥታት ኮመንዌልዝ) የአገር መሪዎች ምክር ቤት ስብሰባም ያካሂዳሉ።
ፑቲን ከታጂኪስታን ፕሬዝዳንት ረሕሞን እና ከአዘርባጃን ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊየቭ ጋርም ውይይት ያደርጋሉ።
በጉብኝቱ ወቅት በርካታ አስፈላጊ ሰነዶች ወደ ስምምነት ይለወጣሉ፤ ከእነዚህም መካከል፦
የውጭ ድንበሮችን ደህንነት ለማጠናከር ያለሙ የትብብር ፕሮግራሞች፣
ሽብርተኝነትን እና አክራሪነትን ለመዋጋት ያለሙ ፕሮግራሞች እንዲሁም
እ.እ.አ እስከ 2030 ድረስ ያለው የወታደራዊ ትብብር ጽንሰ-ሀሳብ ይገኙበታል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ የ"ሲአይኤስ ፕላስ" የተሰኘውን ማዕቀፍ ማቋቋም እና የሻንጋይ ትብብር ድርጅት በኮመንዌልዝ ውስጥ የታዛቢነት ደረጃ እንዲያገኝ ውሳኔዎች ይፀድቃሉ ተብሎ ይጠበቃል ሲል የስፑትኒክ ዘጋቢ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia