ሩሲያ እና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው በኅዳሩ የካይሮ ስብሰባ ቅርበት ያለው ቅንጅትን ይፈጥራሉ ሲሉ በተመድ የሩሲያ መልዕክተኛ ተናገሩ

ሩሲያ እና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው በኅዳሩ የካይሮ ስብሰባ ቅርበት ያለው ቅንጅትን ይፈጥራሉ ሲሉ በተመድ የሩሲያ መልዕክተኛ ተናገሩ
የአፍሪካ ሀገራት የቆየ እና አስተማማኝ አጋር እንደመሆኗ፤ ሩሲያ በምግብ ዋስትና፣ በጤና እና በቀውስ ምላሽ መደገፏን ትቀጥላለች ሲሉ ቫሲሊ ኔበንዚያ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
ሞስኮ በኅዳር ወር በካይሮ በሚካሄደው የሩሲያ–አፍሪካ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ከአፍሪካ መንግሥታት ጋር በአጀንዳው ላይ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አቋም ለማቀናጀት እንደምትጠብቅ ገልጸዋል።
የዲፕሎማቱ ተጨማሪ መግለጫዎች፦
🟠 ፍትህ እና ካሳ፤ ሩሲያ የአፍሪካ ሕብረት እ.ኤ.አ.የ2025 የአፍሪካ እና የአፍሪካ ተወላጆች የፍትሕ ዓመት እስከ 2035 ድረስ እንዲራዘም ትደግፋለች።
🟠 ፀረ-ቅኝ ግዛት አቋም፤ ሞስኮ በሁሉም መልኩ ዓለም አቀፍ የቅኝ ግዛት ተቃውሞ ቀን እንዲቋቋም የሚጠይቅ የተባበሩት መንግሥታት የውሳኔ ሐሳብ እንዲያስተላልፍ ጥሪ ታቀርባለች።
🟠 አፍሪካ-መር፤ የግጭት መፍታት ሂደት በአፍሪካውያን ባለቤትነት መመራት አለበት፡፡ ሞስኮ ለሉዓላዊነት ሙሉ ክብር እንዲሰጥ እና በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎች ውስጥ "3ቱኤ" (በምክር ቤቱ ሦስት የአፍሪካ ተለዋጭ አባላት) እንዲካተቱ አሳስባለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X