ሩሲያ እና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው በኅዳሩ የካይሮ ስብሰባ ቅርበት ያለው ቅንጅትን ይፈጥራሉ ሲሉ በተመድ የሩሲያ መልዕክተኛ ተናገሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሩሲያ እና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው በኅዳሩ የካይሮ ስብሰባ ቅርበት ያለው ቅንጅትን ይፈጥራሉ ሲሉ በተመድ የሩሲያ መልዕክተኛ ተናገሩ
ሩሲያ እና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው በኅዳሩ የካይሮ ስብሰባ ቅርበት ያለው ቅንጅትን ይፈጥራሉ ሲሉ በተመድ የሩሲያ መልዕክተኛ ተናገሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.10.2025
ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና አፍሪካ በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ ተባብረው በኅዳሩ የካይሮ ስብሰባ ቅርበት ያለው ቅንጅትን ይፈጥራሉ ሲሉ  በተመድ የሩሲያ መልዕክተኛ ተናገሩ

የአፍሪካ ሀገራት የቆየ እና አስተማማኝ አጋር እንደመሆኗ፤ ሩሲያ በምግብ ዋስትና፣ በጤና እና በቀውስ ምላሽ መደገፏን ትቀጥላለች ሲሉ ቫሲሊ ኔበንዚያ በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።

ሞስኮ በኅዳር ወር በካይሮ በሚካሄደው የሩሲያ–አፍሪካ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ከአፍሪካ መንግሥታት ጋር በአጀንዳው ላይ ባሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አቋም ለማቀናጀት እንደምትጠብቅ ገልጸዋል።

ዲፕሎማቱ ተጨማሪ መግለጫዎች፦

🟠 ፍትህ እና ካሳ፤ ሩሲያ የአፍሪካ ሕብረት እ.ኤ.አ.የ2025 የአፍሪካ እና የአፍሪካ ተወላጆች የፍትሕ ዓመት እስከ 2035 ድረስ እንዲራዘም ትደግፋለች።

🟠 ፀረ-ቅኝ ግዛት አቋም፤ ሞስኮ በሁሉም መልኩ ዓለም አቀፍ የቅኝ ግዛት ተቃውሞ ቀን እንዲቋቋም የሚጠይቅ የተባበሩት መንግሥታት የውሳኔ ሐሳብ እንዲያስተላልፍ ጥሪ ታቀርባለች።

🟠 አፍሪካ-መር፤ የግጭት መፍታት ሂደት በአፍሪካውያን ባለቤትነት መመራት አለበት፡፡ ሞስኮ ለሉዓላዊነት ሙሉ ክብር እንዲሰጥ እና በፀጥታው ምክር ቤት ውሳኔዎች ውስጥ "3ቱኤ" (በምክር ቤቱ ሦስት የአፍሪካ ተለዋጭ አባላት)  እንዲካተቱ አሳስባለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0