ኢትዮጵያ እና ኬንያ የላሙ ወደብን በተሟላ መልኩ አገልግሎት ለማስጀመር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ እና ኬንያ የላሙ ወደብን በተሟላ መልኩ አገልግሎት ለማስጀመር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
ኢትዮጵያ እና ኬንያ የላሙ ወደብን በተሟላ መልኩ አገልግሎት ለማስጀመር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.10.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ እና ኬንያ የላሙ ወደብን በተሟላ መልኩ  አገልግሎት ለማስጀመር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ

የላሙ ወደብ የላብሴት ፕሮጀክት አካል በመሆኑ ኢትዮጵያ ወደቡ በተሟላ መልኩ አገልግሎት እንዲጀምር ፍላጎት እንዳላት የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ደንጌ ቦሩ ከላሙ ወደብ ማናጀር ኢንጂነር አብዱላሂ ሳማታር በነበራቸው ውይይት ወቅት አንስተዋል።

አክለውም ሀገራቱ ከወደቡ ጋር የሚያገናኛቸውን የየራሳቸውን መንገድ  ለመገንባት በተስማሙት መሠረት ኢትዮጵያ በራሷ በኩል ያለውን የመንገድ መሠረተ ልማት አስቀድማ ገንብታለች ማለታቸውን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ አስታውቋል።

አብዱላሂ ሳማታር በበኩላቸው፣ በኬንያ ወገን የሚገነባው የመንገድ መሠረተ እየተጠናቀቀ በመሆኑ ኢትዮጵያ ወደቡን በተሟላ ሁኔታ መጠቀም እንደምትችል አስታውቀዋል።

ሀገራቱ ለዚሁ ጉዳይ የተቋቋመው የሥራ ግብረ ሃይል ሥራ እንዲጀምር ተስማምተዋል።

ኢትዮጵያ የላሙ ወደብን በመጠቀም በተለይ፦

የአፈር ማዳበሪያን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት እና 

የቁም እንስሳትን ለመላክ እና

ሌሎች ምርቶችን ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ፍላጎት አላት።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ እና ኬንያ የላሙ ወደብን በተሟላ መልኩ አገልግሎት ለማስጀመር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ እና ኬንያ የላሙ ወደብን በተሟላ መልኩ አገልግሎት ለማስጀመር በሚቻልበት ጉዳዮች ላይ ተወያዩ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0