ፑቲን እና ኔታንያሁ በስልክ ተወያዩ
21:06 06.10.2025 (የተሻሻለ: 21:14 06.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፑቲን እና ኔታንያሁ በስልክ ተወያዩ
በኢራን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ዙሪያ በድርድር መፍትሄዎች ላይ እንደመከሩ ክሬምሊን አስታውቋል።
መሪዎቹ በትራምፕ የጋዛ ሰርጥ እቅድ ዐውድ ስለመካከለኛው ምስራቅ ጉዳዮችም አንስተዋል። ፑቲን የፍልስጤም ጉዳይ በዓለም አቀፍ ሕግ ላይ ተመሥርቶ አጠቃላይ እልባት እንዲያገኝ ሩሲያ ያላትን የማይናወጥ አቋም አረጋግጠዋል።
ፑቲን ከኔታንያሁ ጋር ባደረጉት ውይይት ለመጪው የአይሁድ የሱኮት በዓል ለእስራኤል ሕዝብ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። ኔታንያሁ ከቀኑ ቀደም ብለው ለፑቲን የመልካም ልደት ምኞታቸውንም ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X