ኢትዮጵያ ያስጀመረችው የማዳበሪያ ፕሮጀክት በዓመት 1.2 ቢሊዮን ዶላር መቆጠብ እንደሚያስችላት ተገለፀ
20:59 06.10.2025 (የተሻሻለ: 21:04 06.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ያስጀመረችው የማዳበሪያ ፕሮጀክት በዓመት 1.2 ቢሊዮን ዶላር መቆጠብ እንደሚያስችላት ተገለፀ
በዳንጎቴ ግሩፕ ተገንብቶ በቀጣይ ዓመታት ወደ አገልግሎት የሚገባው ፋብሪካ ከፍተኛ ወጪ እንደሚያድን የግብርና ሚኒስቴር ነው ያስታወቀው፡፡
በሚኒስቴሩ የግብርና ኢንቨስትመንትና ግብዓት አቅርቦት ዘርፍ አማካሪ ደረጄ አሳምነው፤ የመንግሥት የማዳበሪያ ወጪ እየጨመረ መምጣቱ ከፍተኛ ተግዳሮት መፍጠሩን ለሀገር ውስጥ ጋዜጣ አንስተዋል።
ፋብሪካው ከ3 ሺ በላይ የሥራ እድል በመፍጠር፣ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚና የግብርና ዘርፉን እንደሚለውጥ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X