በፍራፍሬ ጭማቂ አምራቾች ላይ የተጣለው የኤክሳይዝ ግብር ውሳኔ ታገደ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበፍራፍሬ ጭማቂ አምራቾች ላይ የተጣለው የኤክሳይዝ ግብር ውሳኔ ታገደ
በፍራፍሬ ጭማቂ አምራቾች ላይ የተጣለው የኤክሳይዝ ግብር ውሳኔ ታገደ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.10.2025
ሰብስክራይብ

በፍራፍሬ ጭማቂ አምራቾች ላይ የተጣለው የኤክሳይዝ ግብር ውሳኔ ታገደ

የገንዘብ ሚኒስቴር በዘርፉ ባለድርሻ አካላት የቀረበለትን ቅሬታ ተቀብሎ የገቢዎች ባለሥልጣን ከስድስት ዓመታት በፊት በወጣ ደንብ ላይ ተመሥርቶ እንዲከፈል ያዘዘውን ግብር ማስቀረቱን አስታውቋል፡፡

“ከሸማቾች ያልተሰበሰበውን ዕዳ በአምራቾች ላይ መጫን ፍትሐዊ አይደለም “ ብሏል፡፡

አጋጥሞ የነበረው ውዝግብ፦

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የታሸገ መጠጥ፤ የፍራፍሬ ጭማቂ ተብሎ ለመታሰብ ቢያንስ 30 በመቶ የፍራፍሬ ይዘት ሊኖረው ይገባል ብሎ ነበር፡፡

ባለሥልጣኑ ይህንን መስፈርት አያሟሉም ያላቸውን አምራቾች የ4 ዓመት የኋላ ታክስ እንዲከፍሉም ግዴታ ጥሏል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ውሳኔው የሀገር ውስጥ አምራቾችን ሥራ እንዲያቆሙ እንዳስገደደ እና ከውጭ ከሚገቡ ምርቶች ጋር ያላቸውን ተወዳዳሪነት እንደጎዳ በመግለፅ ቅሬታ አቅርቧል፡፡

የቀረበውን ቅሬታ ተከትሎ የገንዘብ ሚኒስቴር በሕጉ አጻጻፍ ላይ ግልጽነት ተጓድሏል በማለት የገቢዎች ባለሥልጣን ውሳኔን አግዷል።

አምራቾች ምን አሉ?

የኢትዮጵያ መጠጥ አምራች ኢንዱስትሪዎች ማኅበር ዋና ሥራ አስኪያጅ አሸናፊ መርዕድ፤ “ይህ ለዘርፉ ትልቅ እፎይታ ነው” ሲሉ ለሁለት ዓመት ያህል የዘለቀው ክርክር መቋጫ ማግኘቱን ተከትሎ በሰጡት አስተያየት ተናግረዋል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0