ግብፅ የእስራኤል እና ሃማስን ቀጥተኛ ያልሆነ አዲስ ዙር ድርድር ልታስተናግድ ነው
10:32 06.10.2025 (የተሻሻለ: 10:34 06.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ግብፅ የእስራኤል እና ሃማስን ቀጥተኛ ያልሆነ አዲስ ዙር ድርድር ልታስተናግድ ነው
ሁለቱ ወገኖች ዛሬ በዶናልድ ትራምፕ በቀረበው የሰላም የስምምነት እቅድ ዙሪያ ለመወያየት አቅደዋል።
በአሜሪካ ፕሬዝዳንት የሰላም እቅድ መሠረት በዓለም አቀፍ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ትጥቅ ለመፍታት ፈቃደኛ መሆኑን የሚገልጹ ዘገባዎችን ያስተባበለው የሃማስ ልዑካን ቡድን ቀደም ሲል ቦታው ላይ መድረሱን አስታውቋል።
የሃማስ ትጥቅ መፍታት ጉዳይ "በፍልስጤም ማዕቀፍ የሚፈታ የፍልስጤም ጉዳይ ነው" ሲሉ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በድር አብደል አቲ ለአሻራቅ አል-አውሳት ጋዜጣ ተናግረዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤትም ድርድሩ እንደሚካሄድ ያረጋገጠ ሲሆን የእስራኤል ልዑካን ቡድን በስብሰባው ቀን ወደ ሻርም ኤል ሼክ ይጓዛል ተብሎ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X