ሩዋንዳ ለወሲባዊ ጥቃት ሰለባዎች ፍትሕ ለመስጠት የአባትነት ማረጋገጫ ምርመራዎችን ልታስተዋውቅ ነው
17:01 05.10.2025 (የተሻሻለ: 17:04 05.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩዋንዳ ለወሲባዊ ጥቃት ሰለባዎች ፍትሕ ለመስጠት የአባትነት ማረጋገጫ ምርመራዎችን ልታስተዋውቅ ነው
ወደ ሰውነት ክፍል በማይገቡ የህክምና ሂደቶች የሚካሄዱት የቅድመ ወሊድ ምርመራዎቹ፤ ለእናቲቱም ሆነ ለፅንሱ ምንም ዓይነት አደጋ የማያደርሱና ከእርግዝና ስድስተኛው ወር ጀምሮ ሊደረጉ እንደሚችሉ የሩዋንዳ ፎረንሲክ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ቻርለስ ካራንጋ ለአንድ የአካባቢው ጋዜጣ ተናግረዋል።
መንግሥት የምርመራ ሂደት ለማፋጠን በሩዋንዳ የምርመራ ቢሮ በኩል በወንጀል ጉዳዮች ላይ ጥቅም ላይ እንዲውሉ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።
የፅንሱን ዘረመል የያዘ የእናት የደም ናሙና እና ከተጠረጠረው አባት ከጉንጭ የሚወሰድ ናሙና በዘመናዊው የቀጣይ ትውልድ የዘረመል ቅደም ተከተል ማረጋገጭ ቴክኖሎጂ አማካኝነት ውጤቱን ለማመልከት የማነፃፀር ሂደት ይከናወናል ሲሉ ካራንጋ አብራርተዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X