ሶሪያ ከአሳድ መንግሥት መነሳት በኋላ የመጀመሪያውን የፓርላማ ምርጫ አካሄደች
15:08 05.10.2025 (የተሻሻለ: 15:14 05.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሶሪያ ከአሳድ መንግሥት መነሳት በኋላ የመጀመሪያውን የፓርላማ ምርጫ አካሄደች
ዜጎች ከ210 የፓርላማ አባላት 140ውን የመረጡ ሲሆን ቀሪ 70ዎቹን ፕሬዝዳንቱ እንደሚወክሉ ተጠቁሟል።
የሶሪያ የሽግግር ፕሬዝዳንት አህመድ አልሻራ በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ የፓርላማ መቀመጫውን ቁጥር ከ150 ወደ 200 ለማሳደግ የቀረበላቸውን ግዜያዊ የምርጫ ስርዓት የመጨረሻ ረቂቅ ተቀብለዋል።
ሆኖም በነሐሴ ወር በደቡባዊ ሱዋይዳ መንደር ግጭት መባባሱን ተከትሎ አልሻራህ ምርጫውን ለማራዘም ወስነዋል።
ሶሪያ የፓርላማ ምርጫዋን ለመጨረሻ ግዜ ያካሄደችው በአላሳድ የፕሬዝዳንትነት ዘመን እ.አ.አ በሐምሌ 15፣ 2024 ነበር። ከቀድሞ ፕሬዝዳንት አላሳድ ከሥልጣን መነሳት በኋላ ሀገሪቱ በግዜያዊ መንግሥትና ፕሬዝዳንት በሚመራ የሽግግር ማዕቀፍ እየተመራች ትገኛለች።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X