ደቡብዊው ዓለም በዩክሬን ላይ የሚቀርቡ የምዕራባውያን ትርክቶችን ለምን እንደማይቀበል የቡርኪና ፋሶው ባለሙያ አብራሩ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱደቡብዊው ዓለም በዩክሬን ላይ የሚቀርቡ የምዕራባውያን ትርክቶችን ለምን እንደማይቀበል የቡርኪና ፋሶው ባለሙያ አብራሩ
ደቡብዊው ዓለም በዩክሬን ላይ የሚቀርቡ የምዕራባውያን ትርክቶችን ለምን እንደማይቀበል የቡርኪና ፋሶው ባለሙያ አብራሩ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.10.2025
ሰብስክራይብ

ደቡብዊው ዓለም በዩክሬን ላይ የሚቀርቡ የምዕራባውያን ትርክቶችን ለምን እንደማይቀበል የቡርኪና ፋሶው ባለሙያ አብራሩ

የንግድ ሥራ አስፈፃሚው ቴህል ሎኤ ኮናቴ እንዳሉት፣ ደቡባዊ ዓለም (ግሎባል ሳውዝ) በተለይ የአፍሪካ ሀገራት በዩክሬን ጦርነት ገለልተኛ ሆነው መቆየታቸው እና ከሩሲያ ጋር መተባበራቸው ተፈጥሯዊ ነው፤ ይህንን አቋም በቫልዳይ የውይይት ክለብ ላይ የፑቲን መግለጫዎች አስተጋብተዋል።

“የሩሲያው ፕሬዝዳንት ኔቶ ሩሲያን ለመክበብ ባይፈልግ ኖሮ በዩክሬን ያለው ጦርነት ሊቀለበስ ይችል ነበር ብለዋል። ዛሬም ሌላው ዓለም የሚያቀርበው ይህንንኑ ተመሳሳይ ክርክር ነው” ሲሉ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

ምዕራባውያን የሚጭኗቸው የደህንነት ፖሊሲዎች የማንንም ደህንነት የተጠበቀ እንዲሆን አያደርጉም፤ አፍሪካን ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ ይጎዳሉ። ምክንያቱም “አፍሪካ ከምዕራባውያን የሚመጣን የውጭ ጥቃት ለመመከት የሚያስችል በቂ የፖለቲካ እና የደህንነት መዋቅሮች ስለሌሏት ነው” ሲሉ ኮናቴ አክለዋል።

“የአፍሪካ እና የደቡባዊ ዓለም ሀገራት ለምዕራባውያን ባህሪ ምስክሮችና ተጠቂዎች ናቸው፤ ዛሬ ስምምነት ይፈረማል፣ ነገርግን አንዱ ወገን ኃያል ስለሆነ ብቻ ስምምነቱ ከመጣስ አልፎ ፈጽሞ አይከበርም” ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ለማንበብ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0