የእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት የምዕራባውያን ፖሊሲ ሁኔታውን መፍታት እንደተሳነው አብነት ነው - ፑቲን
19:09 02.10.2025 (የተሻሻለ: 19:14 02.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የእስራኤልና ፍልስጤም ግጭት የምዕራባውያን ፖሊሲ ሁኔታውን መፍታት እንደተሳነው አብነት ነው - ፑቲን
ሩሲያ በአውሮፓ ወታደራዊ መጠናከር ላይ የምትሰጠው ምላሽ ብዙ እንደማይቆይ ማንም አይጠራጠርም ሲሉ ፑቲን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በወቅቱ ትራምፕ በስልጣን ላይ ቢኖሩ ኖሮ፣ የዩክሬን ግጭት ሊወገድ ይችል እንደነበር ተስማምተዋል፡፡
ዩክሬንን ላበረታቱና ላስታጠቁ፣ ለአስርተ ዓመታት ከሩሲያና ከሩሲያውያን ጋር እንድትጋጭ ያደረጉ ዩክሬናውያን፣ ለሞስኮ ብቻ ሳይሆን ለዩክሬንና ለሕዝቦቿ ጥቅምም ደንታ ለሌላቸው ሰዎች የሚጣል ዕቃ ናቸው ሲሉ ፑቲን ተናግረዋል።
ኔቶ ወደ ሩሲያ ድንበር ባይጠጋ ኖሮ፣ የዩክሬን ግጭት ላይከሰት ይችል እንደነበር አስምረውበታል፡፡
በዩክሬን ግጭት አለመቆም ዋነኛው ኃላፊነት የአውሮፓ ነው ብለዋል፡፡
የዩክሬን አሳዛኝ ክስተት ለሁላችንም ህመም ነው በማለት አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X