የሌቫንቲን ዝሆን ጥርስ የመጣው ከኢትዮጵያ እንጂ ከግብፅ እንዳልሆነ አዲስ ጥናት አረጋገጠ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሌቫንቲን ዝሆን ጥርስ የመጣው ከኢትዮጵያ እንጂ ከግብፅ እንዳልሆነ አዲስ ጥናት አረጋገጠ
የሌቫንቲን ዝሆን ጥርስ የመጣው ከኢትዮጵያ እንጂ ከግብፅ እንዳልሆነ አዲስ ጥናት አረጋገጠ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.10.2025
ሰብስክራይብ

የሌቫንቲን ዝሆን ጥርስ የመጣው ከኢትዮጵያ እንጂ ከግብፅ እንዳልሆነ አዲስ ጥናት አረጋገጠ

በደቡባዊ ሌቫንት ከ1600 እስከ 600 (አ.አ ከክርስቶስ ልደት በፊት) ይገበያይ የነበረው አብዛኛው የዝሆን ጥርስ ለረጅም ጊዜ ሲታመንበት እንደነበረው ከግብፅ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ እና ከሱዳን አካባቢዎች ጋር ከተያያዙ የአፍሪካ ዝሆኖች የመጣ እንደነበር አዲስ ጥናት አመላከተ።

በሃይፋ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዋ ሓሬል ሾሓት የተመራው እና በጆርናል ኦፍ አርኪኦሎጂካል ሳይንስ የታተመው ይህ ጥናት፤ 624 የዝሆን ጥርስ ቅርሶችን በመተንተን 85% የሚሆኑት ከካርቱም በስተደቡብ ከስድስተኛው የዓባይ ወንዝ ዳር አካባቢ ከሚገኙ የአፍሪካ ዝሆኖች የተገኙ መሆናቸውን አረጋግጧል።

ቀደም ሲል ግብፅ የዝሆን ጥርስ ንግድ ዋና ማዕከል ተደርጋ ብትታይም፣ ግኝቶቹ እንደሚያሳዩት ኑቢያውያንና ከኢትዮጵያውያን ጋር በአንድነት የንግድ መረቦችን በማስቀጠል ማዕከላዊ ሚና ተጫውተዋል። ይህ ሚናቸው በፖለቲካዊ ሁከት ወቅትም ቀጥሏል።

ጥናቱ የኢትዮጵያን በጥንታዊው ዓለም አቀፍ ንግድ ውስጥ ቸል ተብሎ የነበረውን ሚና አጉልቶ አሳይቷል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0