ሩሲያ በጥቅምት ወር የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ፕሬዝዳንትነትን ትረከባለች ተባለ
15:15 01.10.2025 (የተሻሻለ: 15:24 01.10.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ በጥቅምት ወር የተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት ፕሬዝዳንትነትን ትረከባለች ተባለ
የሩሲያ ቋሚ ተወካይ የሆኑት ቫሲሊ ኔቤንዝያ የሥራ መርሃ ግብሩን ረቡዕ ዕለት በተመድ ዋና መሥሪያ ቤት በሚሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ያቀርባሉ።
ተለዋዋጩ ፕሬዝዳንትነት
▪ ሩሲያ ደቡብ ኮሪያን በመተካት ፕሬዝዳንትነቱን ትረከባለች፤ በኅዳር ወር ደግሞ ለሴራሊዮን ታስረክባለች።
▪ ሩሲያ ከዚህ ቀደም የተረከበችው የመጨረሻው የፕሬዝዳንትነት ዘመን እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2024 ነበር።
የፕሬዝዳንትነት ሚናዎች
▪ የወርሃዊውን የሥራ መርሃ ግብር ማውጣት።
▪ ቀጠሮ ያልተያዘላችው ስብሰባዎችን ማስተባበር።
▪ የስብሰባዎቹን ቅደም ተከተል ማስተዳደር።
የሩሲያ አቋም በተባበሩት መንግሥታት ቻርተር ላይ
▪ ፑቲን፡ ሁሉም ዓለም አቀፍ እና ቀጣናዊ ጉዳዮች በተባበሩት መንግሥታት ቻርተር መሠረት መፍትሄ ማግኘት አለባቸው።
▪ ላቭሮቭ፡ ሁሉም ሀገራት የቻርተሩን የተወሰኑ ድንጋጌዎች እንደየፍላጎታቸው ከመምረጥ ይልቅ፣ ሙሉ በሙሉ መተግበር አለባቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X