ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን በምታደርገው ጥረት ከ6 ሀገራት ጋር የቴክኒክ ድርድሯን በስኬት እንደቋጨች ገለፀች
16:01 29.09.2025 (የተሻሻለ: 16:04 29.09.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን በምታደርገው ጥረት ከ6 ሀገራት ጋር የቴክኒክ ድርድሯን በስኬት እንደቋጨች ገለፀች
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከስዊዘርላንድ እና ጃፓን ጋር የተጀመረው የሁለትዮሽ ድርድር በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ እና እስከ መጪው ህዳር 30፤ ከ14 ሀገራት ጋር ድርድር ለመቋጨት መታቀዱን አስታውቀዋል።
በድርድሩ ሂደት ኢትዮጵያን የደገፉ ሀገራት ቁጥር ከ16 ወደ 30 ማደጉንም ገልፀዋል፡፡
ሩሲያ፣ ቻይና እና አርጀንቲና ለኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት ድጋፍ ከሰጡ ሀገራት ውስጥ ተጠቅሰዋል፡፡ እንደ ሚኒስትሩ ገለጻ በድርድሩ ሂደት የቀረቡትን ተጨማሪ 54 የሕግ ሰነዶች ጨምሮ በአጠቃላይ 400 ገደማ ሰነዶች ቀርበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X